ሴቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን መከላከል እንደሚያስፈልግ ተገለፀ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ በየአመቱ ከህዳር 16 ቀን እስከ ታህሳስ 1 ቀን ሚከበረውን የፀረ- ፆታዊ /የነጭ ሪቫን/ ቀን ትናንት ህዳር 24 ቀን 2012 ዓ.ም ሜክሲኮ በሚገኛው የተቋሙ መሰብሰቢያ አዳራሽ አክብሮ ውሏል፡፡
በዕለቱ በዓሉን አስመልክቶ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ ፆታን መሰረት አድርገው የሚፈፀሙ አካላዊ እና ስነልቦናዊ ጥቃቶች የሰው ልጆች መብትን ከመቃረናቸውም በላይ ለከፋ የጤና ችግር የሚዳርጉ በመሆኑ ሁሉም በጋራ ሊከላከለው ይገባል ብለዋል፡፡
በንቃተ-ህግ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የህግ ዳይሬክቶሬት በህግ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ዛሬ ህዳር 18 ቀን 2012 ዓ.ም በሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ሰጥቷል፡፡በስልጠናው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ፣ የክልል ስራ አስፈጻሚዎች፣ ከፍተኛ አመራሮች እና የዲስትሪክት ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ስልጠናውም በዋናነት ከኤሌክትሪክ ጋር የተያያዙ ህጎች፣ መሰረታዊ የህግ ፅንሰ ሃሳቦች፣ የአሰሪና ሰራተኛ ህግ፣ የውልና የውል ኃላፊነት ህግ እንዲሁም የወንጀል ህግ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡
የአዲስ አበባ ዲስትሪቢዩሽን መስመር መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት በመጠናቀቅ ላይ ነው
የአዲስ አበባ ከተማ በፍጥነት ማደግን ተከትሎ የህብረተሰቡ የኃይል ፍላጎት ከመቼዉም ጊዜ በበለጠ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ሆኖም እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት መሸከም የሚችል የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በዚያው መጠን ባለመዘርጋቱ እንዲሁም ያለውንም በማርጀቱ ተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥና መዋዥቅ እንዲሁም የኃይል ብክነት ሲያጋጥም ይስተዋላል፡፡ይህም በከተማዋ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ህብረተሰብ እና በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡
የጋምቤላ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሄደ
የጋምቤላ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2011 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀምና በ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል ምክክር በክልሉ ከሚገኙ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ ህዳር 17 ቀን 2012 ዓ.ም በክልሉ ምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ አከናውኗል፡፡
በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ የአገልግሎት አሰጣጥ ለአገልግሎት ተደራሽነት መሰረት ነው
በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የህብረተሰቡን የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ፍላጎት ማርካት የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ዘርግቶ አገልግሎቱን ተደራሽ ማድረግ ለነገ የሚተው ተግባር አይደለም፡፡