<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>http://www.eeu.gov.et/index.php/feed/am</id>
                                <link href="http://www.eeu.gov.et/index.php/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://eeu.gov.et/) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-09-17T16:59:51+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[የኦፍ-ግሪድ የኢነርጂ አማራጮች ለገጠሪቱ ኢትዮጵያ!]]></title>
            <link rel="alternate" href="http://www.eeu.gov.et/index.php/publication/detail/2559?lang=am" />
            <id>http://www.eeu.gov.et/index.php/2559</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፣ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን በመላ ሀገሪቱ ለማስፋፋትና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመፍጠር ሰፊ ሀገራዊ ንቅናቄ መጀመሩ ይታወቃል ። ሀገሪቱ ያላት መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እና የተበታተነ የሰፈራ ስልት፣ ሁሉንም የሀገሪቱን ክፍል ከዋናው የኤሌክትሪክ መረብ (National Grid) ጋር ለማገናኘት አዳጋች ያደርገዋል።&nbsp;</p><p>&nbsp;</p><p>ይህንን ነባራዊ እውነታ በመገንዘብ፣ ተቋሙ ከዋናው ግሪድ ውጪ ለሚገኙ አካባቢዎች አማራጭ የኃይል ምንጮችን በተለይም ዘመናዊ የፀሐይ ኃይል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ብርሃን የማዳረስ ስራውን በስፋት ተግባራዊ አድርጎታል።</p><figure class="image"><img src="/lfm/1789653489.jpg"></figure><p>&nbsp;</p><p>በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሀገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም ዳይሬክተር አቶ ጥላሁን ብርሃኑ እንደገለጹት፣ በሀገራችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ታሪክን ስንቃኝ፣ ትልቁ መነቃቃት የታየው ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ነው። ተቋሙ ከ19 ዓመታት ወዲህ 'ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም' (NEAP) በተሰኘው መጠነ-ሰፊ እቅድ አማካኝነት ኤሌክትሪክ ያልተዳረሰባቸውን የገጠር አካባቢዎች ብርሃን የማድረስ ስራ ሲሰራ ቆይቷል።&nbsp;</p><p>&nbsp;</p><p>ይህ ፕሮግራም ወደ ስራ ሲገባ በሀገሪቱ ኤሌክትሪክ አግኝተው የነበሩ ቀበሌዎች ብዛት 667 ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው፤ ዛሬ ላይ ግን ይህ አሃዝ ከ8,400 በላይ ደርሷል።በዚህም አሰራር ከ7,600 በላይ የሚሆኑ አዳዲስ የገጠር ቀበሌዎች ከዋናው ግሪድ ጋር ተገናኝተዋል ብለዋል ።</p><p>&nbsp;</p><p>ይሁን እንጂ ከዋናው መረብ እጅግ በጣም ርቀው ለሚገኙ አካባቢዎች የኬብል ዝርጋታ ማካሄድ በኢኮኖሚ አዋጭ ባለመሆኑ፣ ተቋሙ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ከግሪድ ውጪ (Off-grid) የሶላር ኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት ላይ ሙሉ ትኩረቱን አድርጓል።</p><p>&nbsp;</p><p>የሶላር ቴክኖሎጂ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እና ምዕራፎችየዓለም ባንክ (World Bank) ፋይናንስን ጨምሮ በተለያዩ አጋር አካላት ድጋፍ የሚከናወኑ የኦፍ-ግሪድ ፕሮጀክቶች በሶስት ዋና ዋና ምዕራፎች እየተተገበሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል ።</p><p>&nbsp;</p><p>የመጀመሪያው ዙር 12 ቀበሌዎችን ለማገናኘት ታቅዶ፣ 11ኙ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን ቀሪዋ አንዲት ቀበሌ በዚህ ግማሽ በጀት ዓመት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።</p><p><br>ሁለተኛው ዙር በታቀዱት 20 ቀበሌዎች ውስጥ 11ዱ አሁን ላይ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። የ9ኙ ፕሮጀክቶች ተቋራጮች ስራውን በማቋረጣቸው መጓተት ቢታይም፣ ተቋሙ አዳዲስ ተቋራጮችን በመቅጠር ሂደቱን እያፋጠነው ነው።ሌላው አደሌ (ADELE) ፕሮጀክት ሲሆን ወደ 100 የሚጠጉ ቀበሌዎችን የፀሐይ ኃይል ተጠቃሚ የማድረግ ግዙፍ ስራ ሲሆን፣ ከነዚህ ውስጥ 26ቱ ተጠናቀው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል ።&nbsp;</p><p>&nbsp;</p><p>ተቋሙ በዚሁ በጀት ዓመት ተጨማሪ 65 ቀበሌዎችን ለማብራት አቅዷል።በአጠቃላይ በድምሩ 132 የሚሆኑ የገጠር ቀበሌዎች በፕሮግራሙ የታቀፉ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት 46 ቀበሌዎች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።</p><p>&nbsp;</p><p>አቶ ጥላሁን ፤ ማህበራዊ ተቋማት እና የቤተሰብ አባወራዎች ተጠቃሚነትየኤሌክትሪክ ተደራሽነት ለቤተሰብ ብርሃን ከመስጠት ባለፈ፣ መሰረታዊ የሆኑ ማህበራዊ ተቋማት ዘመናዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ማስቻል አለበት።&nbsp;</p><p>&nbsp;</p><p>ከዚህ አኳያ "Stand Alone" በሚባለው እቅድ መሰረት 1,400 የሚሆኑ የገጠር ጤና ተቋማትና ትምህርት ቤቶች የፀሐይ ኃይል ለማቅረብ የጨረታ ሂደቱ ተጠናቆ ወደ ውል ስምምነት መደረሱ የትምህርትና ጤና አገልግሎቱን ጥራት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሻሽለው ይታመናል ሲሉ አቶ ጥላሁን ተናግረዋል ።</p><p>&nbsp;</p><p>በሌላ በኩል፣ የገጠሩ ማህበረሰብ ውድ የሆነውን የኮኔክሽን ክፍያ እንዳይከፍል ለመከላከል ተቋሙ "ያለምንም ክፍያ (በዜሮ ክፍያ) ቆጣሪ መገጠም" የሚል ውሳኔ ያሉት ዳይሬክተሩ፤የህብረተሰቡ ብቸኛ ሀላፊነት ቆጣሪው ከተገጠመ በኋላ የሚጠቀሙትን የኃይል ፍጆታ (Energy Consumption) ሂሳብ መክፈል ብቻ ነው። በነዚህ አካባቢዎች በአማካይ በእያንዳንዱ መንደር እስከ ሦስት ትራንስፎርመሮች (በድምሩ ከ150 እስከ 200 ትራንስፎርመሮች) እየተገጠሙ ይገኛሉ ብለዋል ።</p><p>&nbsp;</p><p>አቶ ጥላሁን አክለውም ፤ &nbsp;በአሁኑ ሰዓት ከ10 ሺህ በላይ አባወራዎች ተጠቃሚ የሆኑ ሲሆን፣ በ2019 በጀት ዓመት ይህንን አሃዝ ወደ 18 ሺህ አባወራዎች ለማድረስ መታቀዱን ገልጸዋል ። ማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶች እና የህብረተሰብ ባለቤትነትኤሌክትሪክ ወደ ሩቅ መንደሮች ሲገባ በህብረተሰቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ የሚታየው ለውጥ ፈጣን መሆኑን አመላክተዋል ።</p><p>&nbsp;</p><p>እንደ እርሳቸው ማብራሪያ ፤ አንደኛ፣ ህብረተሰቡ ተበትኖ ከሚኖርበት አሰራር ወጥቶ ወደ አንድ አካባቢ የመሰብሰብ (Settle የማድረግ) ዝንባሌ አሳይቷል፤ ይህም ለመንግስት ሌሎች መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። ሁለተኛ፣ እንደ ካፌቴሪያ፣ የፀጉር ቤቶች እና አነስተኛ ወፍጮ ቤቶች ያሉ ማይክሮ ቢዝነሶች በመንደሮቹ ውስጥ መበራከት ጀምረዋል።</p><p>&nbsp;</p><p>ይህንን ግዙፍ ኢንቨስትመንት ከስርቆትና ከጉዳት ለመጠበቅ ተቋሙ ማህበረሰቡን ያማከለ የባለቤትነት ስሜት የመፍጠር ስራ ይሰራል ። በተለያዩ መድረኮች ላይ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጀምሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተው ጠንካራ ማሳሰቢያዎችን ይሰጣሉ። ማህበረሰቡም ንብረቱን በንቃት በመጠበቅ እና ህገ-ወጥ ድርጊቶችን በማረም ሃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።</p><p>&nbsp;</p><p>በመጨረሻም አቶ ጥላሁን ፣የ2030 እና የ2035 አምቢሺየስ ግቦችየኢትዮጵያ መንግስት በኤሌክትሪክ ዘርፍ ያስቀመጣቸው ግቦች እጅግ ትልቅ መሆናቸውን ጠቅሰው ፤ በ2030 ዓ.ም የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ወደ 75 በመቶ ለማሳደግ፣ እንዲሁም በ2035 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ 100 በመቶ ለማድረስ ሰፊ ስትራቴጂ መነደፉን አብራርተዋል ።</p><p>&nbsp;</p><p>ይሁን እንጂ ይህንን ግዙፍ ሀገራዊ ህልም እውን ለማድረግ የመንግስት ጥረት ብቻ በቂ አይደለም። ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት ዩኒቨርሳል አክሰስን ለማረጋገጥ እንደ ዓለም ባንክ ያሉ የልማት አጋሮች ድጋፋቸውን ማጠናከር፣ እንዲሁም የግሉ ዘርፍ (Private Sector) በኦፍ-ግሪድ እና ሚኒ-ግሪድ የኤሌክትሪክ ልማት በስፊው እንዲሳተፍ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እና የድጋፍ ፓኬጆችን ማዘጋጀት አስገዳጅ መሆኑን &nbsp;አሳስበዋል።</p><p>&nbsp;</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-09-17T16:59:51+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
