<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<feed xmlns="http://www.w3.org/2005/Atom" xml:lang="am">
                        <id>https://www.eeu.gov.et/feed/am</id>
                                <link href="https://www.eeu.gov.et/feed/am" rel="self"></link>
                                <title><![CDATA[የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት RSS Feeds]]></title>
                            
                                        <subtitle>ይህ RSS feed በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ድረገጽ(https://eeu.gov.et/) ላይ የታተሙ ይዘቶችን ይዟል.</subtitle>
                                                    <updated>2026-05-16T08:42:00+03:00</updated>
                        <entry>
            <title><![CDATA[⚡️ በዘመናዊው ስማርት ቆጣሪ የኤሌክትሪክ አጠቃቀምዎን ያዘምኑ !]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.eeu.gov.et/electrical-tip/detail/2278?lang=am" />
            <id>https://www.eeu.gov.et/2278</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p>&nbsp;</p><p>📟 ስማርት ቆጣሪዎች የትክክለኛ ጊዜ (Real-Time) የኤሌክትሪክ ፍጆታን የሚልኩና መረጃውን በራሳቸው ወደ አገልግሎት ሰጪው ተቋም የሚልኩ ዲጂታል መሣሪያዎች ናቸው።</p><p><br>🌟 ስማርት ቆጣሪ ለምን ያስፈልግዎታል ?</p><p>&nbsp;</p><p>ስማርት ቆጣሪዎች ተጠቃሚዎች ምን ያህል ኃይል እየተጠቀሙ እንደሆነ እንዲረዱ ከማገዙም በላይ የኃይል አጠቃቀማቸውን ተረድተው አላስፈላጊ አጠቃቀምን በመቀነስ ኃይል ማዳን ይችላሉ፡፡</p><p>&nbsp;</p><p>📉 የኤሌክትሪክ ወጪን ለመቀነስ</p><p>&nbsp;</p><p>👉 የኃይል አጠቃቀምን በመከታተል ነዋሪዎችና ፋብሪካዎች የኤሌክትሪክ ብክነትን እንዲቀንሱ ያስችላሉ፣ ይህም ወርሃዊ የፍጆታ ክፍያ በተገቢው መንገድ እንዲከፈል እድል ያስገኛል፡፡</p><p>&nbsp;</p><p>💳 ለትክክለኛ የክፍያ ስርዓት፡-</p><p>&nbsp;</p><p>👉 ስማርት ቆጣሪዎች የኃይል አጠቃቀምን በራሳቸው ስለሚመዘግቡ ከሰው ስህተት የፀዳ ንባብ በመውሰድ ሊከሰት የሚችልን የተሳሳተ የፍጆታ ክፍያን ያስቀራሉ።</p><p><br>📊 ትክክለኛ መረጃ በወቅቱ ለማግኘት</p><p>&nbsp;</p><p>👉 ከነባሮቹ ሜትሮች በተለየ ሁኔታ ስማርት ሜትሮች በወቅቱ መረጃ ይሰጣሉ። ተጠቃሚዎች ከፍተኛ የኃይል አጠቃቀምን በፍጥነት ለይተው እርምጃ እንዲወስዱያስችላሉ፡፡</p><p>&nbsp;</p><p>#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-05-16T08:42:00+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[በወላይታ ሪጅን በተለያዩ አካባቢዎች የመልሶ ግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.eeu.gov.et/news/detail/2277?lang=am" />
            <id>https://www.eeu.gov.et/2277</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የወላይታ ሪጅን የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል በሪጅኑ በተለያዩ አካባቢዎች የመልሶ ግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የመልሶ ግንባታ ፕሮጄክቶቹ ከወናጎ (ዱማርሶ) እስከ ይርጋጨፌ እና ከሀላባ እስከ ሾኔ ያለውን የኃይል መስመር በአዲስ መልክ የሚቀይሩ ናቸው።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ነባርና ለብልሽት ተጋላጭ የነበሩ የእንጨት ምሰሶዎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ኮንክሪት ምሰሶዎች የመተካት ዓላማ ያለው ሲሆን በአሁኑ ወቅት የሚከናወኑት ሥራዎች የመጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የመጀመሪያው የሥራ ክፍል ከወናጎ (ዱማርሶ) እስከ ይርጋጨፌ ያለውን 9.5 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ መስመር የሚሸፍን ሲሆን፣ ለዚሁ ተግባር እንዲውሉ የታቀዱ 296 የኮንክሪት ምሰሶዎች ተከላ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ከምሰሶ ተከላው ጎን ለጎንም በምሰሶዎች ላይ የሚገጠሙ ልዩ ልዩ መለዋወጫዎች (Accessory Fixing) የማጠናቀቅ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የኬብል ዝርጋታ ሥራውን ብቻ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል። ይህ የ9.5 ኪሎ ሜትር መስመር ዝርጋታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ የወናጎ እና የይርጋጨፌ ከተማን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ ቀበሌዎች ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ ያስችላቸዋል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በተመሳሳይ ሁኔታ ከሀላባ እስከ ሾኔ የሚዘልቀውና 33 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የመካከለኛ መስመር መልሶ ግንባታ ሥራ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ነው። በዚህ መስመር ላይ ያለው የኮንክሪት ምሰሶ ተከላ ሥራ ከሰብስቴሽን አካባቢ ካሉ ጥቂት ምሰሶዎች በስተቀር የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ልክ እንደ ወናጎ-ይርጋጨፌ መስመር ሁሉ የመለዋወጫዎች ገጠማ ሥራው ተጠናቆ የኬብል ዝርጋታ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የሾኔ ከተማንና በዙሪያው ያሉ አካባቢዎችን የኃይል አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ከመፍታቱም በላይ፣ ለአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መነቃቃት እንዲሁም ለኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ጉልህ ሚና ይጫወታል።</p><p style="text-align:justify;">በአጠቃላይ በሁለቱም አቅጣጫዎች እየተከናወኑ ያሉት እነዚህ የመልሶ ግንባታ ሥራዎች የተቋሙን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና የመሠረተ ልማት ዘመናዊነት ግብ የሚያሳኩ ናቸው።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የኮንክሪት ምሰሶዎቹ መተካት ከጥንካሬያቸው ባሻገር በወቅቱ ይከሰቱ የነበሩ የአገልግሎት መቆራረጦችን በእጅጉ የሚቀንሱ በመሆናቸው፣ ደንበኞች ይበልጥ ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት እንዲያገኙ መንገድ የሚከፍቱ ይሆናል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-05-16T08:39:17+03:00</updated>
        </entry>
            <entry>
            <title><![CDATA[ጥራት ያለው የኃይል አቅርቦትና የደንበኞች አገልግሎት ለማረጋገጥ የክትትልና ግምገማ ሥርዓት ወሳኝ ነው]]></title>
            <link rel="alternate" href="https://www.eeu.gov.et/news/detail/2275?lang=am" />
            <id>https://www.eeu.gov.et/2275</id>
            <author>
                <name><![CDATA[Ethiopian Electric Utility]]></name>
                            <email><![CDATA[feeds@eeu.gov.et]]></email>

                        </author>
            <summary type="html">
                <![CDATA[<p style="text-align:justify;">ጥራት ያለው የኃይል አቅርቦትና የደንበኞች አገልግሎት ለማረጋገጥ የክትትልና ግምገማ ሥርዓት ወሳኝ ነው - ኢንጂነር ጌቱ ገረመው</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው፤ ተቋሙ ጥራት ያለው የኃይል አቅርቦትና የደንበኞች አገልግሎት ለኅብረተሰቡ መዳረሱን ለማረጋገጥ የክትትልና ግምገማ ሥርዓት ዋነኛው መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">ዋና ሥራ አስፈፃሚው ይህንን ያሉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሪጅናል ኮኦርዲኔሽን ጽሕፈት ቤት የ10 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በተካሄደበት ወቅት ነው።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በግምገማ መድረኩ ላይ በተለይም አገልግሎቱን ለደንበኞች ተደራሽ ከማድረግ ባሻገር፣ የሚቀርበው የኃይል አቅርቦት ጥራቱን የጠበቀ መሆኑን ለማረጋገጥ ግምገማና ክትትል የሥራው ዋነኛ አካል መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በተከታታይ አራት ቀናት በተካሄደው የግምገማ መድረክ ላይ የሪጅናል ኮኦርዲኔሽን ጽሕፈት ቤት ባለፉት አሥር ወራት ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራትና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ግምገማ ተከናውኗል። የተቋሙን የግዢ ሥርዓት ይበልጥ ቀልጣፋ ማድረግና በሥራ ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የአደጋ ሥጋቶችን በመቀነስ ረገድ መከናወን ያለባቸው ተግባራት ተመልክተዋል።</p><p style="text-align:justify;">&nbsp;</p><p style="text-align:justify;">በመጨረሻም በየደረጃው የሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የደንበኞችን እርካታ የሚያረጋግጥ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።</p>]]>
            </summary>
                                    <updated>2026-05-15T08:30:47+03:00</updated>
        </entry>
    </feed>
